የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ባለሞያዎች ደም ለገሱ
የሀረሪ ክልል ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ባለሞያዎች የደም ልገሳ መርሀ-ግብር አካሄዱ።
የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ባለሞያዎቹ በደም ልገሳው ወቅት እንደገለፁት በደም ዕጦት በዜጎች ላይ በተለይ በወላድ እናቶች ላይ የሚደርሰውን ሞት ለመቀነስ ደም መለገሳቸውን ገልፀዋል።
ደም መለገስ የዜጎችን ህይወት ከመታደግ ባለፈ ለለጋሹ ጤና ጠቃሚ በመሆኑ ሁሉም ዜጋ በተለይ ወጣቱ ደም በመለገስ የወገን ህይወትን እንዲታደግ ጥሪ አስተላልፈዋል።
0 Comments