Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

በሐረር ከተማ ተሻሽሎ ወደ ስራ የገባውን የደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ደንብ በመተላለፍ አካባቢ ያቆሸሹ 8 ሆቴሎች በብር መቀጮ ተቀጡ-የሐረሪ ክልል ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት

ሐረር፣ሰኔ 11/2017(ሐክመኮ):-በሐረር ከተማ ተሻሽሎ ወደ ስራ የገባውን የደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ደንብ በመተላለፍ አካባቢ ያቆሸሹ 8 ሆቴሎች በብር መቀጮ መቀጣታቸውን የሐረሪ ክልል ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት አስታወቀ።

የሐረሪ ክልል ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ መሀመድ አብደላ እንደገለፁት ፅ/ቤቱ በክልሉ ተሻሽሎ ወደ ስራ የገባውን የደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ደንብ ተግባራዊ ለማድረግ ጥብቅ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ፅ/ቤቱ እያከናወነው በሚገኘው የቁጥጥር ስራም ደንቡን ተላልፈው የተገኙ 8 ሆቴሎችና ግለሰቦች በብር መቀጮ እንዲቀጡ መደረጉን አስታውቋል።

ፅ/ቤቱ ተሻሽሎ ወደ ስራ የገባው የደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ደንብን በተመለከተ ለማህበረሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን ሲሰጥ መቆየቱንም ገልፀዋል።

የከተማዋን ውበትና ፅዳት ለመጠበቅ ተሻሽሎ ወደ ስራ የገባው የደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ደንብ ተፈፃሚ ለማድረግ ፅ/ቤቱ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ያሉት ሀላፊው ማህበረሰቡም ለደንቡ ተገዢ በመሆን የአካባቢውን ፅዳትና ውበት ሊጠብቅ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፅ/ቤቱ ደንቡን በሚተላለፉ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይ መውሰድ የጀመረውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

en_USEnglish