Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል

ከምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከቀረቡ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች መካከል:-

👉ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአለም አርዓያ የሚሆን እጅግ አስደናቂ ተግባር አከናውናለች

👉በለውጡ መንግስት የባህር በር ጥያቄን ወደ መድረክ ማምጣት ተችሏል። መንግስት እያካሄደ የሚገኘው የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ስራም እጅግ የሚበረታታ ነው፥የባህር በር ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ቢሰጥ

👉በኢትዮጵያ ከከተማ እስከ ገጠር እየተካሄደ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የኢትዮጵያን ገጽታ እጅጉን የሚቀይር ነው፥ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ያለበት ደረጃን በተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጥ

👉ሙስና የሰላማችንና የሀገራዊ እድገታችን ጠንቅ ሆኖ እንዳይቀጥል በመንግስት በኩል የተያዘው አቋም ላይ ምን አቅጣጫ ተቀምጧል

👉የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከፍተኛ እድገት እያሳየ የሚገኝ ቢሆንም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማህበረሰብ በኑሮ ውድነት እየተጎ ነው፤

👉ለወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አንጻር በመንግስት በኩል የተሰሩ መልካም ስራዎች እንደተጠበቁ ሆኖ አሁንም የስራ እድል ፈጠራው ተጠናክሮ ቢቀጥል

👉በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ ታዳጊዎችን ወደ ትምህርታቸው ለመመለስ የተቀመጠ አቅጣጫ ካለ ማብራሪያ ቢሰጥ

👉በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ማህበረሰቡን ሰላም የሚነሱ ሽፍቶችና ጽንፈኞች ንጹሃንን ሲያግቱ፤ ሲገድሉ ይስተዋላልና መፍትሄ ቢቀመጥ

👉 በሀገሪቱ የዋጋ ንረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሸማቹን የመግዛት አቅም እየተፈታተነ ይገኛል። በተለይ የዚህ ተጎጂው የመንግስት ሰራተኛው ነውና በመንግስት በኩል ምን ታስቧል

👉ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚኖረውን ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር እና ክልሎችን እርስ በርስ ለማገናኘት ፈጣን የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ከመገንባት አንጻር ምን ታስቧል

0 Comments

There are no comments yet

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

en_USEnglish