የሀረር ከተማን የጅብ ትርዒት ወደ ዘመናዊ የቱሪስት መዳረሻነት መቀየር መቻሉ ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል-የውጭ አገር ጎብኚዎች
ሀረር፣መስከረም 28/2018(ሀክመኮ):-ሀረር ከተማ የምትታወቅበትን የጅብ ትርዒት ወደ ዘመናዊ የቱሪስት መዳረሻነት መቀየር መቻሉ ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የውጭ አገር ጎብኚዎች ገለፁ።
ጎብኚዎቹ ሐረርን የጎበኙ ጸሐፍት ትርዒቱን አድንቀው የፃፉትን በተግባር እንድንመለከት አስችሎናል ሲሉም ገልፀዋል።
በኢኮ ፓርኩ የተመለከቱት ትርዒት ሐረር ሰዎችና የዱር እንስሳት ተግባብተው የሚኖሩባት ከተማ መሆኗን በተግባር የሚያሳይ ነው።
በተለይ ፓርኩን በዘመናዊ እና ምቹ መንገድ መገንባት መቻሉ ትርኢቱን በምቹ ሁኔታ እንድንታደም አስችሎናል ብለዋል።

0 Comments