የሰላም ጉባኤ ተሳታፊዎች ሀረር ከተማ ገቡ
በሀረር ከተማ በነገው ዕለት የሚካሄደው ሀገር አቀፍ የሰላም ጉባኤ ተሳታፊ እንግዶች ሀረር ከተማ ገብተዋል።
እንግዶቹ ድሬደዋ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳን ጨምሮ የክልሉ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባላት በተገኙበት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
እንግዶቹ በነገው ዕለት በሀረር ከተማ በሚካሄደው ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ ሲሆን በክልሉ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ይመለከታሉ ተብሎም ይጠበቃል።



0 Comments