የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎትን በማስጀመር አገልግሎቶችን ባጠረ ግዜ ለመስጠት ይሰራል-ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ
ሐረር፣ግንቦት 21/2017(ሐክመኮ):-በሐረሪ ክልል የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎትን በማስጀመር ማህበረሰቡ አገልግሎቶችን ባጠረ ግዜ እንዲያገኝ ለማድረግ እንደሚሰራ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ
ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዛሬው እለት የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎትን ለማስጀመር የተመረጠውን ቦታ ተመልክተዋል።
በቀጣይ ለማዕከሉ አስፈላጊውን የመሰረተ ልማት በማሟላት ማህበረሰቡ የተለያዩ አገልግሎቶችን በአጠረ ጊዜ፣ በተሻሻለ ቅልጥፍና እና ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲያገኝ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልፀዋል።

0 Comments