Skip to content Skip to main navigation Skip to footer

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ እየተወያየ ነው

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ እየተወያየ ይገኛል።

በትናንትናው እለት በደማቅ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት የተጀመረው የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በጠዋቱ ክፍለ ጊዜው በጉባኤው አዘጋጅ አብይ ኮሚቴ ሪፖርት እና በሁለተኛው ጉባኤ የስብሰባ ሥነ-ሥርዓት ደንብ ላይ ተወያይቶ አጽድቋል።

ጉባኤው በአሁኑ ወቅት በማዕከላዊ ኮሚቴው በቀረበ ሪፖርት ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሪፖርቱን በውይይት አዳብሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

በቀጣይ መርሀ ግብሩም በቀሪ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎች ያሳልፋል፣ ቀጣይ አቅጣጫዎችንም ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከፓርቲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

0 Comments

There are no comments yet

Leave a Comment

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

amAmharic